Showing posts with label ኪነ ጥበብ. Show all posts
Showing posts with label ኪነ ጥበብ. Show all posts

Saturday, October 21, 2017

እኔስ ሰው አማረኝ






እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ
የምንኩስና ግብር ምን ነበር ምሥጢሩ
የክርስትና ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ
መቃብሩን ክፈቱና አበው ይመስክሩ፡፡

Thursday, February 4, 2016

በአበው ብሂል እንጨዋወት

ረዥም አይደል አጭር፣
ወፍራምም አይደል ቀጭን፣
ታግሎ የጣለኝ ከሰው ደጅ፣
እኔን ያኸል ነው እንጂ፡፡

ጥያቄ፡ ሀ. ሕብረ ቃሉ .......................................................... ነው፡፡
        ለ. ሰሙ …………………………………………………………………. ነው፡፡
        ሐ. ወርቁ ………………………………………………………………. ነው፡፡

Monday, January 4, 2016

በአበው ብሂል እንጨዋወት


እንደምን ዋላችሁ ውድ የማኅቶት እድምተኞች! በማኅቶት ኪነ ጥብብ ገጽ ላይ በአበው ብሂል እንጨዋወት የተሰኘ አበቶቻችን ደስታን፣ ሀዘንን፣ ፍቅርን፣ ቁጭትን፣ … ወዘተ የሚገልጹበት ሀይማኖታዊ፣ ባህላዊ፣ ታሪካዊ፣ማሕበራዊ ጉዳዮችን የሚዳስስ

Friday, January 1, 2016

‹እግዜር እና ጴጥሮስ›› ይህችን ሰዓት ! (1)

ሰሞኑን ነው አሉ
ደጋግ ቅዱሳን በገነት ውስጥ ያሉ
በድንገት በእግዜር ድምጽ ‹‹ተነሱ!›› ተባሉ

ዐይኔን መጽውቱልኝ

ችግሩ ፍዳዬ፣ ደስታው ፌሽታዬ
ሆነን እንኖራለን፣ እንዘልቃለን ብዬ
ስቸረው ስቸረው…

Thursday, December 10, 2015

ወርቅ ሰጥተን ጠጠር እንዳንቀበል


ይህችን ጽሑፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ አማርኛ የሚመስሉ የባዕድ ሀገር ስሞች ትክክለኛ የአማርኛ ትርጓሜዎች የሚል መልእክት በድሬ ትዩብ ላይ ማንበቤ ነው ፡፡
ኢትዮጵያውያ ሀገራችን በዓለም ካሉ ሀገራት ሁሉ የተለየ ከእርሷ የበቀለ የራሷ ብቻ የሆነ ሀገር በቀል ባህል ከነወጉ ፣ ቋንቋ ከነፊደሉ ፣ ቀመር ከነቁጥሩ ፣ ታሪክ ከነክብሩ ፣ ትምህርት ፣ ምርምርና ፍልስፍና ከነተጋባሩ ፣ ጥበብ ከነማዕረጉ ፣ አስተዳደር ከነስልቱ አስተባብራ የያዘች ምልዕት ሀገር ናት ፡፡ ከዚህም ባሻገር ሀገራችን ኢትዮጵያውያ እግዚአብሔር የሚመለክባት የሀይማኖት ደሴት በቅዱሳን ጸሎት የምትጠበቅ ሀገረ እግዚአብሔር ናት ፡፡ ሕዝቧም በሀይማኖት ጸንቶ የሚኖር ሕዝበ እግዚአብሔር ነው ፡፡

Friday, November 27, 2015

ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ

 
" በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤ ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። "
1ኛ ቆሮንቶስ 13፥1-7
 
      (ከይልቃል ፍቅሬ የተወሰደ)